January 19 2023

የመጀመሪያ ምንባብ

ቲቶ 3፡ 4~7
4
ነገር ግን የአዳኛችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር በተገለጠ ጊዜ፣ 5ስላደረግነው የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነን። ያዳነንም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው፤ 6ይህንም መንፈስ እግዚአብሔር በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእኛ ላይ አትረፍርፎ አፈሰሰው፤ 7ይኸውም በጸጋው ጸድቀን የዘላለምን ሕይወት ተስፋ ይዘን ወራሾች እንድንሆን ነው።

        

ሁለተኛ ምንባብ

1ኛ ዮሐ 5፡ 5~12
5
ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ከሚያምን በስተቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማነው?

6በውሃና በደም የመጣው ይህ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በውሃና በደም እንጂ በውሃ ብቻ አልመጣም። የሚመሰክረውም መንፈስ ነው፤ መንፈስ እውነት ነውና። 7ስለዚህ ሦስት ምስክሮች አሉት። 8እነርሱም መንፈሱ፣ ውሃውና ደሙ ናቸው፤ ሦስቱም ይስማማሉ። 9የሰውን ምስክርነት ከተቀበልን፣ የእግዚአብሔር ምስክርነት ከዚያም ይልቃል፤ ይህ ስለ ልጁ የሰጠው የእግዚአብሔር ምስክርነት ነውና። 10በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን ሁሉ በልቡ ምስክር አለው፤ ማንም እግዚአብሔርን የማያምን ሁሉ እግዚአብሔር ስለ ልጁ የሰጠውን ምስክርነት ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል። 11ምስክርነቱም ይህ ነው፤ እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት ሰጠን፤ ይህም ሕይወት ያለው በልጁ ነው። 12ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።

ወንጌል

ሉቃ 3፡ 21~38
የኢየሱስ መጠመቅና የትውልድ ሐረጉ

21ሕዝቡ ሁሉ ከተጠመቀ በኋላ ኢየሱስም ተጠመቀ፤ እየጸለየም ሳለ ሰማይ ተከፈተ፤ 22መንፈስ ቅዱስም በአካላዊ ቅርጽ እንደ ርግብ በእርሱ ላይ ወረደ፤ ከሰማይም፣ “የምወድህ ልጄ አንተ ነህ፤ በአንተ ደስ ይለኛል” የሚል ድምፅ መጣ።

23ኢየሱስ አገልግሎቱን ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ነበር፤ ሕዝቡም እንደ መሰላቸው የዮሴፍ ልጅ ሆኖ፣

የኤሊ ልጅ፣ 24የማቲ ልጅ፣

የሌዊ ልጅ፣ የሚልኪ ልጅ፣

የዮና ልጅ፣ የዮሴፍ ልጅ፣

25የማታትዩ ልጅ፣ የአሞጽ ልጅ፣

የናሆም ልጅ፣ የኤሲሊም ልጅ፣

የናጌ ልጅ፣ 26የማአት ልጅ፣

የማታትዩ ልጅ፣ የሴሜይ ልጅ፣

የዮሴፍ ልጅ፣ የዮዳ ልጅ፣

27የዮናን ልጅ፣ የሬስ ልጅ፣

የዘሩባቤል ልጅ፣ የሰላትያል ልጅ፣

የኔሪ ልጅ፣ 28የሚልኪ ልጅ፣

የሐዲ ልጅ፣ የዮሳስ ልጅ፣ የቆሳም ልጅ፣

የኤልሞዳም ልጅ፣ የኤር ልጅ፣

29የዮሴዕ ልጅ፣ የኤልዓዘር ልጅ፣

የዮራም ልጅ፣ የማጣት ልጅ፣

የሌዊ ልጅ፣ 30የስምዖን ልጅ፣

የይሁዳ ልጅ፣ የዮሴፍ ልጅ፣

የዮናም ልጅ፣ የኤልያቄም ልጅ፣

31የሜልያ ልጅ፣ የማይናን ልጅ፣

የማጣት ልጅ፣ የናታን ልጅ፣

የዳዊት ልጅ፣ 32የእሴይ ልጅ፣

የኢዮቤድ ልጅ፣ የቦዔዝ ልጅ፣

የሰልሞን ልጅ፣ የነአሶን ልጅ፣

33የአሚናዳብ ልጅ፣ የአራም ልጅ፣

የአሮኒ ልጅ፣ የኤስሮም ልጅ፣ የፋሬስ ልጅ፣

የይሁዳ ልጅ፣ 34የያዕቆብ ልጅ፣

የይስሐቅ ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ፣

የታራ ልጅ፣ የናኮር ልጅ፣

35የሴሮህ ልጅ፣ የራጋው ልጅ፣

የፋሌቅ ልጅ፣ የአቤር ልጅ፣

የሳላ ልጅ፣ 36የቃይንም ልጅ፣

የአርፋክስድ ልጅ፣ የሴም ልጅ፣

የኖኅ ልጅ፣ የላሜህ ልጅ፣

37የማቱሳላ ልጅ፣ የሄኖክ ልጅ፣

የያሬድ ልጅ፣ የመላልኤል ልጅ፣

የቃይናን ልጅ፣ 38የሄኖስ ልጅ፣

የሤት ልጅ፣ የአዳም ልጅ፣

የእግዚአብሔር ልጅ።

Previous
Previous

January 22 2023

Next
Next

January 15 2023